tg-me.com/theamazingquran/2799
Last Update:
ደስ የምትባል ታሪክ ናት 👇👇✨✨✨
አውሮፓ ውስጥ የሚገኝ ዩኒቨርስቲ...
አዳራሹ በተማሪዎች እና ጥሪ በተደረገላቸው ምሁራን እንግዶች ጥቅጥቅ ብሎ ሞልቷል። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት አጠር ያለ ንግግር ካደረገ በኋላ የሀገሪቱን ሊቀ-ጳጳስ ወደ መድረክ ጋብዞ ወረደ።
ጳጳሱ ረዘም ያለ ሰዐት ንግግር አደረገ'ና፦ «ከመድረክ ከመውረዴ በፊት እዚህ አዳራሽ ውስጥ የምትገኙ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮችን 2 ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ።»
አዳራሹ ውስጥ ፀጥታ ሰፈነ፤ ሁሉም ከመድረክ የሚሰነዘረውን ጥያቄ ለማደመጥ ትኩረቱን ከመድረኩ ላይ አደረገ።
ከአደራሹ ውስጥ የሚገኙ ውስን ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ተማሪዎችም ከጳጳሱ ለሚሰነዘረው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ራሳቸውን አዘጋጁ።
ጳጳሱ ጥያቄውን ጀመረ፦
«እናንተ ሙስሊሞች 'ሙሀመድ በአንድ ሌሊት ቅፅበት ውስጥ ከመካ እስከ እየሩሳሌም ከእየሩሳሌም እስከ ሰማየ-ሰማያት ሄዶ መጥቷል' ብላችሁ ታምናላችሁ። ይህ እንዴት ይሆናል?»
ከተማሪዎቹ መሀል አንድ ወጣት ብድግ አለ። ለተሰነዘረለት ጥያቄ ማሰላሰያ እንኳን ሳያሻው መልሱን ወደ መድረኩ ሰደደ፦«አንተ ከቤትህ ቁጭ ብለህ በምታዳምጣት የሬድዮ ሞገድ የአሜሪካንን ድምፅ ትሰማለህ፤ ሲያሻህ የአውስትራልያን ጣብያ ቀይረህ ታዳምጣለህ።
የሰው ልጅ በሰራው ሞገድ ቤትህ ቁጭ ብለህ በቅፅበት ውስጥ የአለምን አፅናፍ ካዳረስክ የሰውን ልጅ የፈጠረው ጌታ በአንድ ሌሊት ሙሀመድን ቢያንሸራሽረው ምን ይደንቃል...?»
አዳራሹ ለረጅም ደቂቃዎች በጭብጨባ ደመቀ...። ጳጳሱ ወጣቱን አድንቆት ወደ ቀጣዩ ጥያቄ ተሸጋገረ፦
«እስላሞች 'ነፍስን ሁሉ በመግደል ስራ ላይ የተሰማራ አንድ መልዓክ ነው' ትላላችሁ።
ለምሳሌ፦ በመቶዎች የሚቆጠሩ የባህር መንገደኞች በሜድትራንያን ውቅያኖስ ላይ ሰጥመው ቢሞቱ እና በተመሳሳይ ሰዐት ህንድ ውቅያኖስ ላይም በርካታ የመርከብ ተጓዦች ቢሞቱ እንዴት ነው የሞት መልአክ በዝያ ቅፅበት ሁለቱም የአለም አፅናፍ ጋ ሊደርስ የሚችለው...?»
አዳራሹ ውስጥ የተሰበሰበው ህዝብ የሙስሊሞቹን መልስ ሊያዳምጥ አዳራሹ ላይ ፀጥታን አሰፈኑ፤ ያ ልጅ ዳግም ብድግ አለ፦
«በዚህ በምንኖርባት ሰፊ ከተማ ውስጥ ስንት የመብራት አምፖሎች ይገኛሉ...? ብዙ ናቸው። ያን ሁሉ አምፖሎች አንድ የመብራት ሀይል ሰራተኛ ቢሮው ቁጭ ብሎ በአንድ ሴኮንድ ማጥፋት አይችልም...?»
ጳጳሱ፦ «ይችላል...»
ወጣቱ፦ «ታድያ የመብራት ሀይል ሰራተኛ በቅፅበት ውስጥ ያን ሁሉ አምፖሎችን ማጥፋት ከቻለ፤ የአላህ ሰራተኛ ነፍሶችን በቅፅበት ማጥፋት እንዴት ይሳነዋል..!!!»
BY ¶በላጭ ሕዝቦች¶
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/theamazingquran/2799